Sunday 22 September 2013

የገሐነም ደጆች አይችሏትም

የእግዚአብሔርን ታምር ተመልከቱ ቦታው ሶርያ ነው የቤተክርስትያኑ ስም Saydania ይባላል::
እንደተለመደው የዘወትር ፀሎቷ ለህዝቧም ለዓለምም እያደረሰች ባለችበት ሰዓት አንድ ሰው ወደ 
መነኩሴዋ እማሁይ Marina Almaloof ቀርቦ 
"ሥዕለት ለመስጠት ነበር፤ እባከዎ ይሄን ብር ሳጥን ውስጥ ያስገቡልኝ፤ በእጅ የያዘውን 160ሳ.ሜ
የሆነውን ሻማ ይሄን ደግሞ በስዕለ ማርያም ፊት ያብሩልኝ፤ እኔ በጣም ሰለምቸኩል ነው" ይልና 
በፍጥነት ይወጣል:: መነኩሴዋም ክብሪት አነሱ አቤቱ የሰራዊት ጌታ ስዕለቱን ተቀበለው አሉ፡፡
ክብሪቱን ጫሩ ሻማው ጫፍ አቀረቡት ሻማው ሳይቃጠል ክብሪቱ ተቃጥሎ አለቀ በድጋሜ ሞከሩ፤
ሞከሩ፡፡ ሻማው ባለመቃጠሉ እየተገረሙ ከወደ ውጪ ጩኸት ተሰማ፡፡ መነኩሴዋም ወጡ ከታች
መጨረሻ ደረጃው ላይ አንድ ሰው ወድቆ የሞተ ሰው ያያሉ፡፡ "ይሄ አሁን ስለት የሰጠኝ ሰውየ ነው"
አሉ፡፡ ስልክ ለሶርያ ፖሊስ ተደወለ፤ በፍጥነት መጡ ነገሩ ተጣራ፡፡ እስኪ ሻማው? አለ ፖሊስ፡፡ 
ሻማው ተመረመረ በውስጡ ዳይናሜት TNT የተባለ አደገኛ ተቀጣጣይ ፈንጆች የተሞላ ሆኖ ተገኘ
ሰውየውን የሚያውቅ ሠው አልተገኝም፡፡ ሰውየው በልብ ድካም ነው የሞተው ተባለ፡፡ ወላዲተ አምላክ
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ህዝቧንም ቤተክርስትያኑንም ታደገች፡፡
እንዲህ ናት የኛ እመቤት ንጽህተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሣን ንዕድ ክብርት ብጽዕት ድንግል ማርያም!
ጸሎቷና በረከቷ ሁሌም ይጠብቀናል፡፡ እልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልል...
ልመናዋ ክብሯ የልጇም ቸርነት በመላው ሕዝበ ክርስቲያን ላይ ይደር አሜን!!!

No comments:

Post a Comment